Hibret Bank Image

ሕብረት ባንክ እና የአዲስ አበባ እድሮች ምክር ቤት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ

ሕብረት ባንክ እና የአዲስ አበባ እድሮች ምክር ቤት በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ግንቦት 03 ቀን 2015 ዓም በሕብረት ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርመዋል፡፡

በሕብረት ባንክ በኩል ስምምነቱን የፈረሙት የባንኩ ስትራቴጂና ቴክኖሎጂ ም/ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አንዷለም ኃይሉ እንደገለፁት እድር ለኢትዮጵያውያን ትልቅ ሀገራዊ እሴት በመሆኑ ባንኩ የአዲስ አበባ እድር ምክር ቤትን የማገዝ እድል በማግኘቱ ክብር ይሰማዋል፡፡

በአዲስ አበባ እድሮች ምክር ቤት በኩል ስምምነቱን የፈረሙት የአዲስ አበባ እድሮች ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ታምራት ገብረማርያም በበኩላቸው ሕብረት ባንክ እድሮችን ለማገዝ ፈቃደኛ የሆነ ቀዳሚ ባንክ መሆኑ አርአያነት ያለው ተግባር መሆኑን ጠቅሰው የተጀመረው አጋርነት ለውጤት እንደሚበቃ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል ፡፡

በሁለቱ ተቋማት መካከል የተደረሰው ስምምነት ስልታዊ አጋርነትን በመፍጠር ለእድሮች ምክር ቤት አባላት ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት የሚያግዝ ነው፡፡

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

Similar Posts